የ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ኣመራሮች ከ ዩኒቨርሲቲው መምህራን ጋር ውይይት ኣደርጉ

 መዩ ከፍተኛ ኣመራሮች መምህራን ውይይት

 የ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ኣመራሮች ከ ዩኒቨርሲቲው መምህራን ጋር ውይይት ኣደርጉ
ይህ መድረክ "ትውልድ በ መምህር ይቀረፃል : ሀገር በ ትምህርት ይበለፅጋል" በሚል መሪ ቃል ከ መቐለ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጋር ውይይት እንዲደረግ በ ትምህርት ሚኒስትር በቀረበው የውይይት ሰነድ ላይ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ መድረክ ነው።
በዚህ የውይይት መድረክ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ኣመራሮች ከ ዩኒቨርሲቲው ኣስተማሪዎች ጋር በመነሻ ሰነዱ ላይ ትኩረት ኣድርገው የተወያዩ ሲሆን በመድረኩ የተገኙት ተሳታፊዎችም ሰነዱን መሰረት ኣድርገው በዩኒቨርስትያችን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማነፃፀርና በመገምገም መሻሻል ኣለባቸው ያሉዋቸው ሃሳቦች በመጨመር ዉይይቱ ተዘግቷል።

 መዩ ከፍተኛ ኣመራሮች መምህራን ውይይት 2 መዩ ከፍተኛ ኣመራሮች መምህራን ውይይት 1